Thursday 16 April 2015

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከግብፁ ፕሬዚዳንት ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ

የሕዳሴ ግድብን መሠረት በማድረግ የስምምነት ፊርማ ሱዳን ላይ አድርገው ለይፋዊ ጉብኝት ወደ ሀገራችን የመጡትና ከሀገራችን ከፍተኛ መሪዎች ጋር ተገናኝተው ስለ አጠቃላይ የጋራ እሴቶችና የጋር ጥቅሞች አብሮ ተባብሮ ማሳደግ ስለሚቻልበት ሁኔታ እጅግ መልካም በሆነ ሁኔታ ሲነጋገሩና ስምምነት ላይ የደረሱትን የግብፁ ፕሬዚዳንት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትም ውጤታማና ለሁለቱም ሀገራትና ሕዝቦች በሚበጅ ጉዳዮች ዝግ በሆነ መልኩ ውይይት አድርገው የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል፡፡
233

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን መጋቢት 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን ሆቴል ተገናኝተው ያደረጉት ውይይት መልካም የሚባሉና ለሁለቱም ሀገር ሕዝቦች ብሎም ለመላው አፍሪካ የሚበጅ አጀንዳዎች በማንሳት መሆኑ ቅዱስነታቸው ከውይይት በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አብራርተዋል፡፡ የውይይቱ ዋና ዋና አጀንዳዎችን በተመለከተ ቅዱስ ፓትርያርኩ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ስለ ዓባይ ግድብ በጋራ መጠቀምን፣ ስለ ሁለቱም ሀገራት ሰላም፣ ስለ ሁለቱም ሀገራት ሕዝቦች አንድነት፣ ስምምነትና የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት በአግባቡ ተጠብቆ ማስቀጠል ስለሚቻልበት ሁኔታ በተመለከተ ሰፊ የሆነ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውንና ፕሬዚዳንቱም ቀና የሆነ የስምምነትና የትብብር መንፈስ እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ከላይ የተገለፁ ሐሳቦችን በተመለከተ በመርህ ደረጃ ሙሉ በሙሉ መስማማታቸውንና የሁለቱም ሀገራት ታሪካዊ የሆነ ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጠንካራ ግንኙነት አሁንም በመተማመን ላይ ተመሥርቶ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ መግለፃቸውን በወቅቱ ለመረዳት ተችሏል ፡፡

No comments:

Post a Comment